Cyber Power Tigray Media (CPT media )

ሳይበር ፖወር ትግራይ ሚድያ – ነፃን ህዝባውን ሚድያ እዩ!


Follow us on:
አማርኛ ዜና
0

ሩሲያ በዩክሬኗ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤት እና የደኅንነት ሕንጻን በሚሳኤል ደበደበች

በምስራቃዊ ዩክሬን በምትገኘው ዲኒፕሮ ከተማ ትናንት ሌሊት [አርብ] ሩሲያ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች። በጥቃቱ የጋራ መኖሪያ ቤት እና አንድ የደኅንነት መሥሪያ ቤት ሕንጻ ኢላማ ተደርገዋል።

የከተማዋ ባለሥልጣናት እንዳስታወቁት በጥቃቱ ቢያንስ 9 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። ሁለቱ ሕጻናት መሆናቸው ታውቋል።

የቢቢሲ የዘገባ ቡድን በስፍራው ተገኝቶ እንዳረጋገጠው የጋራ መኖሪያ ቤት ጣሪያ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተደርምሷል።

ንብረትነቱ የዩክሬን የደኅንነት መሥሪያ ቤት የሆነ ግዙፍ ሕንጻም የጥቃቱ ሰለባ ሆኗል

ጥቃቱን የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ “የሩሲያ የሚሳኤል ሽብር” ብለውታል።

ዘሌንስኪ ከተደረመሰው ሕንጻ የሚወጣን ጭስ እና በጎዳና ላይ የሚንቦገቦግ የእሳት ነበልባልን በቴሌግራም ገጽ አጋርተዋል።

ክስተቱን ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ የአካባቢው ባለስልጣናትንና የተመረጡ የካቢኔ አባላትን በመጥራት ለአስቸኳይ ስብሰባ መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

bbc

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *